“
ሀትሪክ በነገው እትሟ
የሚወዷት ጓጉተውም የሚያነቧት የዘወትር ማክሰኞ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ በገበያ ላይ ትውላለች፤ ሀትሪክ በእትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
በሀገር ውስጥ ዘገባዋ በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW አምዷ የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተር እና ጋዜጠኛ የሆነው ይስሀቅ በላይ በአሁን ሰዓት በአልቢትርነት ሙያው የራሱንና የአገራችንን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ እያስጠራ ያለውን ስኬታማውን ኢንተርናሽናል አልቢትር በአምላክ ተሰማን መውጫና መግቢያ አሳጥቶት ያነጋገረውን ቃለ-ምልልስ የምታስነብቦት ሲሆን ሌሎችም መረጃዎችን ጋዜጣዎ ትሰጦታለች፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ከበአምላክ ጋር በነበራት ቆይታ አልቢትሩ ለተጠየቀው ጥያቄ በጥቂቱ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷታል፡፡
“የህዝቡ የደስታ ስሜትና ያሳየኝ ድጋፍ የበለጠ እንድሰራ እንቅልፍ እንዳጣም አድርጎኛል የሚልና
“የሚቀጥለውን የአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ በመምራት ደስታው የተነጠቀውን ህዝቤን መካስ እፈልጋለሁ፡፡ ያለው ይገኝበታል።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋም ለእናንተ ከምታቀርብሎት ውስጥ ለባርሴሎና ፊርማውን ያኖረው አንቷ ግሬዝማን “ከሜሲ ጎን ተሰልፌ ለመጫወት እጅግ በጣም ጓጉቼያለሁኝ” ስላለበት ምላሽ ስለ አርሰናሉ ስፔናዊ አዲስ ፈራሚ ሴባልስ ለክለቡ ስለሚጨምርለት አቅምና ተጨዋቹ ወደ ቡድኑ በመምጣቱ ስለተሰማው ስሜት የማንቸስተር ሲቲው RAHEEM STERLING
“የአዲሱ አመት የሊጉ ፉክክር ከመቼም ጊዜ ይበልጥ ጠንካራ እንደሚሆን ስለመናገሩና የሊቨርፑሉ ግዙፉ ተከላካይ VIRGIL VAV DIJK የወርቅ ኳስ ተሸላሚ መሆን ይችላል ወይንስ አይችልም በሚል ዘገባ ላይ ነገ ሀትሪክን ያገኟታል፤ ሀትሪክ ሌሎችም ሊያነቡት የሚችሉ ዘገባዎች አሏት፤ ሀትሪክ አታምልጥዎት፡፡
ሀትሪክ በነገው እትሟ የሚወዷት ጓጉተውም የሚያነቧት የዘወትር ማክሰኞ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ በገበያ ላይ ትውላለች፤ ሀትሪክ በእትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
Hatricksport team