ሀትሪክ ነገስ? ምን ታስነብቦታለች
ሀትሪክ ስፖርት ነገ ለንባብ ስትበቃ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ትቀርባለች።
በሀገር ውስጥ:- ከፍተኛ ተወዳጅነትን እያተረፈችበት በመጣችሁ ዘ ቢግ ኢንተርቪው ዓምዷ በፕሮፌሽናል ተጨዋችነት ለግብፁ አስዋን ክለብ የሚጫወተው የቀድሞው የመከላከያ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨዋች እንደዚሁም ደግሞ ለብሄራዊ ቡድናችንም የተጫወተው ዑመድ ኡኩሪ ስለ ፕሮፌሽናል ተጨዋችነት ዘመን ቆይታው እና ወደ ጠንካራው የግብፅ ሊግ ውስጥም መጥቶ መጫወት ስለሚቻልበት ሁኔታ ይናገራል።
ሊግ ከእዚህ ዘገባ ውጪም በግብፅ ሊግ ይጫወት ስለነበረው እና በውሰትም ወደ ሳውዲ አረቢያ ስለተሰጠው ጋቶች ፓኖምም አናግራው የምትለው አላት። ከዛም ባሻገር ሌላም ምርጥ ምርጥ ዘገባዎችን ታስነብቦታለች።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋም የአርሰናሉ ኦባማያንግ “ተራራቁ ብንባልም ከሲቲ ጋር በሚኖረን ጨዋታ በግሌና ከጓደኞቼ ጋር ለመደነስ እሞክራለው” ስለማለቱ ዲኤስቲቪ የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎችን በቀጥታ ማስተላለፍ ሊጀምር ስለመሆኑ ቲሞ ቨርነር ቼልሲን በመጨረሻ ምርጫው ስለማድረጉ እና የማንቸስተር ዩናይትዱ ኦዲዮን ኢግሃሎ በዘረኝነት ዙሪያ ስለሰጣቸው አስተያየቶቹ ሀትሪክ ታስነብቦታለች። ሀትሪክ በመዝናኛ አምዷም የሚወዱት ዘገባ አላት። አታምልጦት። ያንብቧት። ሀትሪክን በቴሌግራም እና ድህረገጽ Hatricksport.net ይከታተሏት።
የሀትሪክ የፊት ለፊት ምስል ይህን ይመስላል።