በሮቤል አለማየሁ
የኢትዮጵያ ኘሪምየር ሊግ 5ኛ ሳምንት ጨዋታ መካከል ሶዶ ስታዲየም ላይ ክትፎዎቹን ያስተናገዱት ወላይታ ድቻዎች 1-0 በሆነ ውጤት ተረተዋል።
በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም 9:05 ሲል በጀመረው ጨዋታ ወላይታ ዲቻ የሜዳ ላይ 3ኛ ጨዋታውን ሲያደርግ፡ በመጀመሪያ ሳምንት ሲዳማ ቡናን 2-0 እንዲሁም በ3ኛ ሳምንት ከቅ.ጊዮርጊስ ጋር አቻ ከተለያየበት የዛሬው ወላይታ ድቻ ጨዋታ የተመልካቹን ቀልብ ያልሳበ ነበር። በአንፃሩ ግልፅ የጨዋታ ስትራቴጂና አጨዋወት የነበራቸው ክትፎዎቹ ወልቂጤ ከተማዎች ነበሩ።
- ማሰታውቂያ -
ወላይታ ዲቻ በ4-4-2 አሰላለፍ በአንፃሩ ወልቂጤ ከነማ በ4-3-2-1 አሰላለፍ ነበር የተጠቀሙት፡፡የጦና ንቦቹ ወላይታ ድቻዎች ኳስ ተቆጣጥረው ለመጫወት ቢሞክሩም ከተወሰነ ቅብብል በሗላ ይበላሽባቸው ነበረ።
ፀጋዬ አበራ በ10 ደቂቃ ከ16 ከሀምሳ ውጭ መሬትለመሬት አክርሮ የመታውን ግብ ጠባቂው ያዳነበት የወልቂጤው ጫላ ተሺታ በ32ኛው ደቂቃ በመልሶ ማጥቃ በክንፍ በኩል ከበረኛው ጋር ተገናኝቶ ወጋ አድርጓት ወደ ወጭ ወጣበታለች።
ወልቂጤ ከነማ በጥብቅ መከላከል እንዲሁም በመልሶ ማጥቃት ረጃጅም ኳሶች ለጃኮ አራፋትና ጫላ ተሺታ አልፎ አልፎ በመጣል ግብ ለማስቆጠር ይሞክሩ ነበር። ይህም ተሳክቶላቸው የመጀመሪያው 45 ከመጠናቀቁ በፊት ጫላ ተሺታ የራሱ ጥረት ታክሎበት ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡
በመጀመሪያው አጋማሽ ጃኮ አራፋት በወልቂጤ በኩል፣ ፀጋዬ አበራ በወ.ዲቻ በኩል ከዕረፍት በፊት የግብ ሙከራ ያደረጉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
ብዙም ሳይቆይ በተደጋጋሚ የዲቻን ተከላካዮች ከመልሶ ማጥቃት በሚያገኘው ኳሶች ሲያስጨንቅ የነበረው ጫላ ተሺታ በቆንጆ አጨራረስ የማሸነፊያ ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡ በሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ በወላይታ ዲቻ በኩል ቸርነት ጉግሳ ከ16 ካሀምሳ ውጭ አክርሮ መቶ ግብ ጠባቂው ይድነቃቸው ለጥቂት ካወጣበት ኳስ ውጭ ብዙም ሙከራ ሳይደረግበት በደጋፊ ብስጭትና አልፎ አልፎ በሚሰማ ዝማሬ ተጠናቋል፡፡