ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ
ፍልሚያ በ3 የክልል ክለቦች መርሃ ግብር
መሆኑ አጓጊ ሆኗል፡፡
መሪው ፋሲል ከተማ አዳማ ላይ ከአዳማ ከተማ
ጋር 1ለ1 ተለያይቶ ሁለት ወሳኝ ነጥቦችን
ቢጥልም በግብ ክፍያ የሊጉን መሪነት አሁንም
ይዟል፡፡ በአዳማው ፍልሚያ ሙጂብ ቃሲም
ለፋሲል ከተማ ቡልቻ ሹራ ለአዳማ ከተማ
ባስቆጠሯቸው ግቦች በ53 ነጥብና 29 ግብ
ሊጉን ሲመራ መቐለ ላይ ደቡብ ፖሊስን 4ለ0
የረታው መቐለ 70 እንደርታ በእኩል 53
ነጥቦችና 19 ግቦች ከኢትዮጵያ ቡና ጋር አቻ
ወጥቶ ያጣውን 2 ነጥብ ዳግም አግኝቶ ፉክክሩ
ላይ ነፍስ ዘርቶበታል፡፡ ለገ/መድህን ኃይሌ
ቡድን ማውሊ ሳውሊ 2 ግብ ሲያስቆጥር
ቀሪዎቹን አማኑኤል ገ/ሚካኤልና ያሬድ
ብርሃኑ አስቆጥረዋል፡፡ ድሬደዋን በሀብታሙ
ገዛኸኝ ግብ 1ለ0 የረታው ሲዳማ ቡና በ52
ነጥብ ፋሲል ከነማና መቐለ 70 እንደርታ ላይ
ደረስኩ እያለ ጫናውን በማሳደር ላይ ይገኛል፡
፡በቀሪው መርሃ ግብሮች ፋሲል ከነማ ከቅ/ጊዮርጊስ በሜዳው ከስሁል ሽረ ጋር ከሜዳው
ውጪ ይጫወታል፡፡ መቐለ 70 እንደርታ
በበኩሉ ከመከላከያ ጋር ከሜዳው ውጪ
ከድሬደዋ ጋር በሜዳው ሲጫወት ሲዳማ ቡና
ከሜዳው ውጪ ስሁል ሽረን በሜዳው ደግሞ
ወልዋሎ አዲግራትን ይገጥማል፡፡
29ኛ ሳምንት መርሀ ግብር
ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2011
04:00 ወልዋሎ ዓ/ዩ ከ ስሑል ሽረ
09:00 ባህር ዳር ከተማ ከ ጅማ አባ ጅፋር
09:00 ወላይታ ድቻ ከ አዳማ ከተማ
09:00 ደቡብ ፖሊስ ከ ኢትዮጵያ ቡና
09:00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ
09:00 ደደቢት ከ ሲዳማ ቡና
09:00 ፋሲል ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ
09:00 መከላከያ ከ መቐለ 70 እንደርታ