በግብፅ ሊግ ያለፉትን በርካታ ዓመታት በስኬት መጓዝ የቻለው የዋልያዎቹ ፈርጥ ሽመልስ በቀለ የቡድኑን አሸናፊነት ያጠናከረቸውን ጎል ማስቆጠር ችሏል ።
ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው የግብፅ ሊግ የሽመልስ በቀለ ቡድን አል መካሳ ከቀናት በፊት አሰልጣኝኑ የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ዲድዬ ጎሜዝ ከሰናበተው እስማኤሊያን 4 ለ 1 ባሸነፉበት ጨዋታ ሶስተኛውን ግብ ለቡድኑ አስቆጥሯል ።
ሽመልስ በቀለ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራት የመጀመሪያው ግብም መሆኗ ተገልጿል ።