ናይጄሪያዊው የ26 ዓመት አጥቂ አሌክስ ኦሮትማል የኬኒያውን ኤኤፍሲ ሊዮፓርድ ለቆ በዛሬው ዕለት ለሁለት ዓመት በሚቆይ የውል ስምምነት ቅዱስ ጊዮርጊስን ተቀላቅሏል።
ክለቡ ትላንትና ከቶጎ ከጋና እና ከኬንያ ሶስት ተጫዋቾችን ያስፈረሙት ጊዮርጊሶች ዛሬ ደግሞ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈርሟል። አሌክስ ኦርትማል ለሳምንታት ከፈረሰኞቹ ጋር ደብረዘይት በሚገኘው የይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ውስጥ ሙከራውን ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ በ1.5 ሚሊዮን የዝውውር ዋጋ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተቀላቅሏል።
ፎቶ © የቅዱስጊዮርጊስ የፋዊ ገፅ