በ19ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ በቆሼ አካባቢ በተፈጠረው አደጋ ህይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችን በማሰብ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የተጀመረው ጨዋታ ያለግብ በአቻ ውጤት ተጠናቆል::
ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን በአዲስአበባ ስታዲየም ሲያስተናግድ በጨዋታው ባለሜዳው ኢትዮጵያ ቡና የተሻለ እንቅስቃሴ ሲያደርግ በ33ኛው ደቂቃ ላይ ሲሳይ ቶሊ አህመድ ረሺድ ላይ በሰራው ጥፋት ኢትዮጵያ ቡና የፍፁም ቅጣት ምት ሲያገኘ ጋቶች ፖኖም መቶ በጨዋታው ድንቅ እንቅስቃሴ ያሳየው የአዳማ ከተማው ግብ ጠባቂ ጃኮ ፔንዛ አድኖበታል ፡፡
በሊጎ ደረጃ ሰንጠረዥ ላይ ኢትዮጵያ ቡና በ32 ነጥብ እና በ10 የጎል ክፍያ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ አዳማ ከተማ በ31 ነጥብ በ4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ኘሪሜየር ሊጉ እሁድ እና ሰኞ ሲቀጥል፡-
# | ክለብ | ተጫ | ልዩ | ነጥብ | |
---|---|---|---|---|---|
1 | ቅዱስ ጊዮርጊስ | 17 | 20 | 35 | |
2 | ኢትዮጵያ ቡና | 19 | 10 | 32 | |
3 | ሲዳማ ቡና | 18 | 5 | 32 | |
4 | ደደቢት | 18 | 9 | 31 | |
5 | አዳማ ከተማ | 19 | 4 | 31 | |
6 | ፋሲል ከተማ | 18 | 4 | 26 | |
7 | አርባምንጭ ከተማ | 18 | 0 | 24 | |
8 | ሀዋሳ ከተማ |
18 | -1 | 21 | |
9 | ወልዲያ ከተማ |
18 | -1 | 21 | |
10 | መከላከያ | 18 | -5 | 21 | |
11 | ወላይታ ድቻ |
17 | -5 | 21 | |
12 | ኢትዮ ኤሌክትሪክ | 18 | 0 | 20 | |
13 |
|
18 | -4 | 20 | |
14 | ድሬዳዋ ከተማ | 18 | -10 | 17 | |
15 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ | 18 | -13 | 15 | |
16 | አዲስ አበባ ከተማ | 18 | -10 | 11 |