የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በ2011 ዓ.ም ከሚያካሂዳቸው አገር አቀፍ እና ኢንተርናሽናል ውድድሮች መካከል ከዚህ በታች የተገለፁትን ውድድሮች :-
v የኢትዮጵያ ሴቶች ኘሪሚየር ሊግ የ2011 ዓ.ም የሁለቱም ዲቪዚዮኖች ውድድር ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል፡፡
v የኢትዮጵያ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በ2010 ዓ.ም የኘሪሚየር ሊግ ወንዶች አሸናፊ በሆነው በጅማ አባ ጅፋር ክለብ እና በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ አሸናፊ በሚሆነው ክለብ መካከል ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል፡፡
v የኢትዮጵያ ወንዶች ኘሪሚየር ሊግ የ2010 ዓ.ም የውድድር አፈፃፀም ግምገማ እና የ2011 ዓ.ም የዕጣ ማውጣት ሥነስርዓት መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል፡፡
- ማሰታውቂያ -
v የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኬንያ አቻው ጋር መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም በ10፡00 ሰዓት በባህር ዳር ስታዲየም እንደሚካሄድ የሚጠበቀው ጨዋታ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የስታዲየም ለውጥ እንደተደረገ የሚገለጸው መረጃ የተሳሳተ ሲሆን ውድድሩ በባህር ዳር ስታዲየም የሚከናወን ይሆናል ፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን