የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግን በመካከለኛ እና ደቡብ ምዕራብ ምድብ ሐ ተቀላቅሎ የነበረው የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ እግር ኳስ ክለብ በበጀት እጥረት ምክንያት ሊፈርስ ከጫፍ መድረሱ እየተነገረ ይገኛል።
የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ክለብ ለቡድኑ ተጨዋቾች እስካሁን
የ3 ወር ደመወዝ እንዳልከፈላቸው እየተነገረ ሲሆን ክለቡና ተጨዋቾቹ በሚለያዩበት ሁኔታ ላይም ከእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ጋር ሁለቱ አካላቶች መነጋገራቸው እና የ3 ወር ደመወዛቸው ሊሰጣቸው እንደሆነም እየተነገረ ይገኛል።
የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ክለብ መፍረሱ ሙሉ ለሙሉ ከተረጋገጠ በህጉ መሰረት ማን ተክቶት ይወዳደራል የፌዴሬሽኑ ህግ የሚመልሰው ይሆናል።
ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል
Hatricksport team