ከወሎ ሰፈር ወደ ቄራ ሲያቀኑ የኢትዮጲያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ
ዋና ጽ/ቤት ወይም የሳውዲአረቢያ ኤምባሲ ጋር ሳይደርሱ የሚያገኙት ባለ 8 ፎቅ ህንፃ በተለይ ከሰኔ በዃላ
የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል::
ከፊፋ በተገኘ ድጋፍ እስከ 120 ሚሊየን ብር የሚያወጣው
ህንጻ. በ95 ሚሊየን ብር. ለመግዛት የተስማሙት. አመራሮቹ
ወደ 7. የሚጠጉ ህንጻዎችን ከተመለከቱ በዃላ መሆኑ ታውቋል::
ፌዴሬሽኑ ወደ 13 ሚሊየን ብር ለሻጩ የቅድሚያ ክፍያ የሰጠ ሲሆን የርክክብ ሂደቱ በ3ወር ጊዜ ውስጥ የሚያልቅ እንደሆነ መረጃዎች ያስረዳሉ::
አመራሮቹ በቅርቡ በዚህ ህንጻ ግዢ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል