የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ እጣ ማውጣት ስነ ስርአት ዛሬ ይደረጋል
◂
ለ11ጊዜ የሚያካሂደው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ዛሬ በኢትዮጵያ ሆቴል ከቀኑ 5:00 ጀምሮ እንደሚካሄድ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን አሰታውቋል።
ስድስት የአዲስ አበባ ክለቦች እና ሁለት ተጋባዥ ክለቦችን ጨምሮ ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 13 በሚከናወነው በዚህ ውድድር አዳማ ከተማ እና በተጨማሪ የሚጋበዘውን ክለብ ዛሬ በእጣ ማውጣት ስነ-ስራዓቱ እሚገለፅ መሆኑ ተነግሯል፡፡