የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሚያወዳድራቸው ውድድሮች መካከል አንደኛው የሆነው በቀድሞ ስያሜው ‹‹ብሄራዊ ሊግ ›› በአሁኑ መጠሪያው ‹‹አንደኛ ሊግ›› የደንብ ውይይት እና እጣአወጣጥ ስነስርአት ዛሬ ተከናውኗል።
በፕሬዝዳንቱ አቶ ጁነዲን ባሻ መክፈቻ ንግግር የተጀመረው ውይይት ፣ ። የ2009 ዓ.ም ውድድር አመት ሪፖርት ቀርቧል።
ከዚህ ሪፖርት መጠናቀቅ በኋላ የዳኞች ኮሚቴ ተወካይ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በአመቱ ለምን ያህል ዳኞች የአካል ብቃት ምዘና ፈተና እንደተሰጠ በሪፖርቱ ውስጥ ተጠቅሷል። በዚህም መሰረት ለ215 ዳኞች የአካል ብቃት ምዘና ፈተና ተሰጥቷል።
በተጨማሪም በውድድር አመቱ አንድ ዳኛ ከፍተኛ 12 ጨዋታዎችን እንዲሁም ዝቅተኛ 7 ጨዋታዎችንአጫውቷል። ከዚም በማስከተል የዳኞች ሪፖርት ተጠናቆ ወደ ፀጥታ ኮሚቴ ሪፖርት አምርቷል።
ከዚህ በማስቀጠልም የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው ሪፖርት ማሰማት የጀመረ ሲሆን በስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለት የጎፋ ባሪንቼ 6 ነጥብ እና 100 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበት እንደነበር እና ነጥብ መቀነስ ክለቡ ላይ ብቻ ሳይሆን አካባቢው ላይ የሚያመጠውን ተፅዕኖ ከግምት በማስገባት 50 ሺህ ብር እንዲሆን ተደርጎ የነጥብ ቅነሳውን ሽረናል ሲሉ አብራርተዋል።
የደንቡ ክፍተት ችግር እያመጣብን ነው፤ ስለዚህም የጥፋት ዝርዝር እና ከፍተኛ እና ዝቅተኛ ጥፋቶች በግልፅ መቀመጥ አለበት ሲሉ ተወያዮቹ ሀሳባቸውን አንፀባርቀዋል።
ለ3 የውድድር አመታት የሚያገለግል ደንብ የወጣ ሲሆን ክለቦቹ በተወካዮቻቸው አማካኝነት ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። የሚዲያ ትኩረት፣ ዳኝነት እና ስፖርታዊ ጨዋነት ትልቅ የመወያያ ርዕስ ሆነው ተነስተዋል።
በስፖርታዊ ጨዋነት ዙሪያ የተቀጡ ቡድኖች የተሻለ ነጥብ ተሰጥቷቸዋል ምክንያቱ ምንድነው, ኮከብ ግብ አግቢ እና ተጫዋች የተሰጣቸው ነገር ምንድነው? እንደ ተቋም የሰጣቸው እውቅና ምንድነው ግልፅ ቢሆን ተብሏል።
ከሰአት በኋላ በነበረው የውይይት ጊዜ
13ቱ ተሰብሳቢዎች ሀሳባቸውን ገልፀው ምላሾች የተሰጡ ሲሆን በስብሰባው ድርጊቱ ሲፈፀም ቦታው ላይ ሁሉ ያልነበሩ ተጫዋቾች ተቀጥተውብናል የሚል ቅሬታ ተነስቶ የነበረ ሲሆን የዲሲፒሊን ኮሚቴ ተወካዪ በቀረበልን ሪፖርት መሰረት ነው ሲል ሲሉ መልሰዋል።
የውድድሩ መጀመሪያ ቀን ላይ ሀሳብ ተነስቶ የመጀመሪያው ቀን ጥቅምት 18 የነበር ሲሆን ህዳር 3 ለመጀመር ሀሳብ ቀርቦ በመጨረሻም ህዳር 25/2010 እንዲጀመር ተወስኗል።
በመጨረሻም ስለ ወራጅ እና አላፊ ቡድኖች ሀሳብ የተነሳ ሲሆን ቀደም ሲል ከየምድቡ አንደኛ አንደኛ የሚወጡት ቡድኖች በቀጥታ አልፈው አንድ ቡድን የተሻለ ነጥብ ያመጣው ተደምሮ ለከፍተኛ ሊግ ያልፉ ነበር በአሁኑ የውድድር አመት ግን ከየምድቡ ከ1~3 የወጡት በቀጥታ አልፈው የተሻለው አራተኛ ተቀላቅሎ የማጠቃለያ ውድድር ይደረጋል ተብሏል። የቀኑ ውሎም የምድብ ድልድይ በማውጣት ተጠናቋል፡፡
ምድብ -ሀ
1. አራዳ ክ/ከተማ
2. አምቦ ከተማ
3. ወሊሶ ከተማ
4. አሶሳ ከተማ
5. ንስር
6. ጋምቤላ ዩኒቲ
7. አ/አ ፖሊስ
8. ዱከም ከተማ
9. ቱሉ ቦሎ
10. መቱ ከተማ
11. ነቀምት ከተማ
12. ሆለታ ከተማ
13. ጋምቤላ ከተማ
ምድብ -ለ
1.ቢሾፍቱ ከተማ
2.ሞጆ ከተማ
3.ባቱ ከተማ
4.ወንጂ ስኳር
5.ካሊ ጅጅጋ
6.ድሬዳዋ ጨርቃጨርቅ
7.ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ
8.መተሃራ ስኳር
9.ኢትዮ-ሶማሌ ልዩ ፖሊስ
10.ሀረር ከተማ
11.ካዳባ አፋር
12.ሀረር አባድር
13.ገላን ከተማ
ምድብ -ሐ
1. ላስታ ላሊበላ
2. ዳሞት ከተማ
3. ትግራይ ዋልታ ፖሊስ
4. አማራ ፖሊስ
5. ትግራይ ውሀ ስራ
6. ራያ አዘቦ
7. ሶሎዳ አድዋ
8. አምባ ጊዮርጊስ
9. ደባት ከተማ
10. ደባርቅ ከተማ
11. መርሳ ከተማ
12. ሰሜን ሸዋ ደ/ብርሃን
13. አዊ አምፒልታቅ
14. የጁፍሬ ወልድያ
ምድብ-መ
1.ጉለሌ ክፍለ ከተማ
2.አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ
3.ጨፌ ዶንሳ
4.ቂርቆስ ክፍለ ከተማ
5.ቦሌ ክፈፍለ ከተማ
6.ቦሌ ገርጂ ዩኒየን
7.ጎጃም ደብረማርቆስ
8.ናኖ ሁርቡ
9.ሰንዳፋ በኬ
10.አቃቂ ክፍለከተማ
11.ንፋስ ስልክ ክፍለከተማ
12.ለገጣፎ 01
13.ልደታ ክፍለከተማ
- ማሰታውቂያ -
ምድብ -ሠ
1.ሀዲያ ሌሞ
2.አርሲ ነገሌ
3.ሺንሺቾ ከተማ
4.ጋርዷላ
5.ኮንሶ ኒዮርክ
6.ሮቤ ከተማ
7.ቡሌ ሆራ ከተማ
8.ወላይታ ሶዶ
9.ጪንቻ ከተማ
10.ጎፋ ባሬንቼ
11.ጂንካ ከተማ
12.ጎባ ከተማ