ደሞዝ አልተከፈለንም በሚል ምክንያት ከአንድ ሳምንት በላይ ልምምድ አቋርጠው የነበሩት ደደቢቶት ትላንትና ና ዛሬ መደበኛ ልምምዳቸውን ሰርተዋል።
የራትናአ ወርና ከዛ በላይ ደሞዝ ያልተከፈላቸው ተጨዋቾቹ በቅርብ ቀናት ውስጥ ሙሉ ደሞዛቸው እሚከፈላቸው ይሆናል።በቅርቡ ሁለት ቅጣቶች ከፌዴሬሽኑ የተላለፈበት ደደቢት ከኢትዮጵያ ፕሪምየር የመሰናበት ዕድሉ የሰፋ ነው።
ስፖንሰር ከሚያደርጉት ድርጅቶች ቃል የተገባለትን ብር ያገኘው ደደቢት በ25ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ባህርዳር ከተማን በሜዳው ትግራይ ስታድየም እሚያስተናግድ ይሆናል።