የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉንና 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ያካሂዳል።
ከፕሬዝዳንቱ በተጨማሪ የፊፋ ዋና ጸሐፊ ፋትማ ሳሙራ ለዚሁ ጉባኤ አዲስ አበባ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንድምኩን አላዩ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል።
ጂያኒ ኢንፋንቲኖ እና ፋትማ ሳሙራ በጉባኤው ላይ በእግር ኳስ ስፖርት ልማት ላይ ያተኮሩ የሃሣብ ልውውጦች እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
በተለይም ዋና ጸሐፊዋ የፊፋ ክፍለ አህጉራዊ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በአዲስ አበባ በሚቋቋምበት አግባብ ዙሪያ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ ጋር ለመምከር ኘሮግራም ይዘዋል፡፡
- ማሰታውቂያ -
ፊፋ በአዲስ አበባ ጽህፈት ቤት ከመክፈት በተጨማሪ ተከታታይ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር እርስቱ ይርዳ፣ ሚኒስትር ዴኤታው ተስፋዬ ይገዙ፣ እንዲሁም የካፍ ኘሬዝዳንት ኢሣ ሃያቱ እና ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች ለእንግዶቹ አቀባበል እንደሚያደርጉላቸው ይጠበቃል።