ድሬድዋ ከተማ በዝውውር መስኮቱ ከዘሪሁን አንሼቦ፣ዋለልኝ ገብሬና አማኑዔል ተሾመ ጋር ዛሬ በይፋ የተለያየ ሲሆን በነሱ ምትክም አዳዲስ ተጫዋቾችን እያስፈረመ ይገኛል።
በሁለተኛው የሊጉ የውድድር አጋማሽ ላይ ጠንክረው ለመገኘት በርካታ ተጫዋቾችን እያስፈረሙ የሚገኙት ድሬድዋ ከተማዎች ሄኖክ ኢሳያስን ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል ::
ከአሰልጣኝ ስምኦን አባይ ጋር ከተለያዩ በሃላ ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት ብርቱ ፍክክር እያደረጉ የሚገኙት
ድሬድዋዎ ከተማዎች በዝውውር መስኮቱ ምንያምር ጴጥሮስን ጨምሮ እስካሁን አራት ተጫዋቾችን ማስፈረም ችለዋል ።