ፋሲል ከነማ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ትናንት የታንዛኒያውን አዛም 1-0 አሸንፈው ከአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር በስምምነት መለያየታቸው ይፋ ሁኗል ።
ፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ስዩም ከበደን በይፋ የቀጣዩ የአፄዎቹ አሰልጣኝ አድርጎ ሾሟል ። አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የትናንትናውን የፋሲልና የአዛም ጨዋታ በባህርዳር ስታዲየም ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን ከ15 ቀናት በኋላ በታንዛኒያ ዳሬሰላም ከተማ ለሚካሄደው የመልስ ጨዋታ የአፄዎቹን የሚያዘጋጁ ይሆናል ።
አሰልጣኝ ሥዩም ከበደ ከዚህ ቀደም ሰበታ ከተማ ፣ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ አዲስ አበባ ከተማና መከላከያን ያሰለጠኑ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዋሊያዎቹንና ሉሲዎቹን በምክትልና በዋና አሰልጣኝነት አሰልጥኗል ።