ሳምንታዊ ባለቀለም የስፖርት ጋዜጣ የሆነችው ሀትሪክ ስፖርት እንደ ተለመደው ነገ ማክሰኞ ህዳር 5/2010 ዓ.ም በማለዳው በእጅዎ ልትገባ መሰናዶዋን አጠናቅቃለች፡፡ ለመሆኑ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ይሆን?
– ከሀገር ውስጥ፡- በቅርቡ የዓለም ወጣቶች ዋንጫንና የአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜን በመሀል ዳኝነት በመምራት የሀገራችንን ስም ከፍ አድርጎ ለማስጠራት የቻለው ኢንተርናሽናል አርቢትር በአምላክ ተሰማ ከታሪካዊው ተልዕኮው መልስ ከሀትሪክ ስፖርት ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ ጋር ምርጥ የሚባል ሰፊ ቆይታን አድርጓል፡፡ አስገራሚ ቃለ-ምልልስ ነው፡፡ ይወዱታል፡፡
– “Oldies but Goodies” በሚለው ተወዳጅ አምዳችን ላይ እንግዳችን በመሆን ወደ ኋሊት ወስዶ ትዝታውን የሚያስቃኘን ባለተረኛ የቀድው የምድር ጦር፣ የመብራት ሀይል፣ የኢትዮጵያ ቡና እና የብ/ቡድናችን ዝነኛ ግብ ጠባቂ በለጠ ወዳጆ ነው፡፡ በጨዋታ እያዋዛ ትዝታውን ይተርክልናል፤ እንዳያመልጥዎት
ከባህር ማዶ፡- የቀድሞው የማን.ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ኤድዊን ቫንደርሳር ያልተሰሙ ምስጢሮች፣ ኦሊቪዬ ዥሩ እና አርሰናል ሊለያዩ ይሆን? ቲዎ ዋልኮት ራሱን ለውድድር የሚያዘጋጀው እንዴት ነው? ዳኒ አልቬስ ከማን.ሲቲ ይልቅ ፒ.ኤስ.ዠን ለምን ሊመርጥ ቻለ? እነዚህንና ሌሎችንም መረጃዎች ከመዝናኛ ወሬዎች ጋር ይዛላችሁ ትመጣለች፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን ከድረ-ገፃችን www.hatricksport.com ማግኘት ይችላሉ፤ ነገ ማክሰኞ ጥቅምት 5/2010 ዓ.ም ለንባብ የምትበቃው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፤ መልካም ንባብ