በሀገር ውስጥ ዘገባዋ The Big Interview በሚለው ተወዳጅ አምዷ የቀድሞ የባቡር፣ የጉና ንግድ፣ የኢትዮጵያ ቡና፣ የሙገር፣ የመተሐራ ስኳር፣ የሰበታ ከነማ፣ የደደቢት እና የኢትዮጵያ የወንዶችና የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበረውን ኢንስትራክተር አብርሃም ተክለሀይማኖትን የግል ህይወትና የስልጠና ውጣ ውረድን አስመልክቶ የጋዜጣው ኤክሲዩቲቭ ኤዲተርና ዋና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ይስሃቅ በላይ ለአሰልጣኙ ሰፋ ያለ ቃለ-ምልልስን አድርጎለት ምላሹን ሰጥቷል፤ ለመሆኑ ኢንስትራክተር አብርሃም ተክለሀይማኖት ለሀትሪክ ምን ብሎ ይሆን?
ሀትሪክ በሌላ የሀገር ውስጥ ስፖርት መረጃዋም የሸገር ደርቢ ጨዋታን አስመልክቶ ከግጥሚያው በኋላ የሁለቱ ክለብ አሰልጣኞች የሰጡትን አስተያየት የምታቀርብሎት ሲሆን ከእነሱ በተጨማሪም የቅዱስ ጊዮርጊሱ ተከላካይ ሳላህዲን ባርጌቾና የኢትዮጵያ ቡናው ተከላካይ ተካልኝ ደጀኔም ከጨዋታው በኋላ የሰጡትን ምልልስም የምታስነብቦት ይሆናል፡፡ ሀትሪክ ተጨማሪ መረጃዎችንም ይዛሎት ቀርባለች፤ ያንብቧት፤ አታምልጦት፡፡
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዎቿስ ምን ይዛ ወጥታ ይሆን፡- ሀትሪክ በነገው እትሟ ይዛሎት የቀረበችው በአጓጊው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮና የሊጉ መሪ ሊቨርፑል አርሰናልን ተፋልሞ በሰፊ ግብ ስላሸነፈበት ጨዋታና ስለ ፊርሚኖ ሀትሪክ ስለሰራበት ብቃት እንደዚሁም ደግሞ ስለማንቸስተር ሲቲና ማንቸስተር ዩናይትድ ድል፤ እና ሌሎችንም የሚወዷቸውን ዘገባዎች የምታስነብቦት ይሆናል፡፡
የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል
ሀትሪክ ስፖርትን በገበያ ላይ ጠብቋት በሳምንት አንድ ቀን ዘወትር ማክሰኞ ለንባብ የምትበቃው ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገም ለእናንተ ውድ አንባቢዎች ጣፋጭ ዘገባዎችን ልታስነብቦት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሳ ወደማተሚያ ቤት አምርታለጭ፡፡ ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
Hatricksport team