ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ
የሚወዷት፤ በጉጉት የሚጠብቋት ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞም እናንተን በንባብ ልታገኝ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡
ሀትሪክ በነገው እትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
በሀገር ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW አምዷ የሀትሪክ ስፖርት ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተርና ጋዜጠኛ የሆነው ይስሀቅ በላይ ላለፉት በርካታ ዓመታት በክለብና በብሄራዊ ቡድን የእግር ኳስ ተጨዋችነትም ሆነ የአሰልጣኝነት ሙያ ላይ በመሰማራት አብዛኛው ህይወቱን ያሰለፈውንና በአሁን ሰዓት ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ክለብን ለማሰልጠን በመስማማት ፊርማውን ላኖረው አመለ ሸጋው ፋሲል ተካልኝ የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርቦለት የሰጠውን ምላሽ ጋዜጣዋ ታቀርብሎታለች፡፡ ፋሲል ምን ብሎ ይሆን ሀትሪክን ያንብቧት።
ሀትሪክ ስፖርት በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባዋም በአፍሪክ ክለቦች የኢንተርናሽናል የውድድር መድረክ ሀገራችንን በመወከል ስለተሳተፉት መቐለ 70 እንደርታና ፋሲል ከነማም መረጃ አላት፤ ከእነዚህ መካከል ፋሲል ከነማ የታንዛኒያውን አዛም ክለብ ባሸነፈበት ጨዋታ ዙሪያ ለቡድኑ የድሉን ጎል ያስቆጠረው በዛብህ መላዮ የሚለው አለው። ተከታተሉት፤ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ተጨዋቾች የደሞዝ ክፍያ ዙሪያም የተጨዋቾች ደሞዝ ከ50 ሺ ብር መብለጥ የለበትም ተብሎ በተወሰነው ውሳኔ ዙሪያም እየተፈጠሩ ባሉት ጉዳዮች ላይም ሀትሪክ መረጃን ትሰጦታለች፤ ሀትሪክ አታምልጦት፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በባህር ማዶ ዘገባዋም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ውድድር በይፋ መጀመርን አስመልክቶ በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት ስለተካሄዱት ታላላቅ ጨዋታዎች ዙሪያ በተለይ ማንቸስተር ዩናይትድ ቼልሲን እንደዚሁም አርሰናል ኒውካስትልን ባሸነፉበት እና ሌሎች ግጥሚያዎችን አስመልክተን የሚወዱትን ዘገባ አቅርበንሎታል።
የሀትሪክ ስፖርት የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል።
ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ የሚወዷት፤ በጉጉት የሚጠብቋት ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞም እናንተን በንባብ ልታገኝ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡
![](https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2019/08/IMG_20190812_191841_791.jpg?resize=860%2C860&ssl=1)
Hatricksport team