ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ
የሚወዷት፤ በጉጉት የሚጠብቋት ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞም እናንተን በንባብ ልታገኝ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡
ሀትሪክ በነገው እትሟ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
በሀገር ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW አምዷ የሀትሪክ ስፖርት ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተርና ጋዜጠኛ የሆነው ይስሀቅ በላይ ላለፉት በርካታ ዓመታት በክለብና በብሄራዊ ቡድን የእግር ኳስ ተጨዋችነትም ሆነ የአሰልጣኝነት ሙያ ላይ በመሰማራት አብዛኛው ህይወቱን ያሰለፈውንና በአሁን ሰዓት ደግሞ ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ ክለብን በማሰልጠን ላይ እሚገኘው እና በአሁን ሰዓት ኘሮፌሽናል ተጫዋቾች ማሀበር ፕሬዝደንት በመሆን እየሰራ እሚገኘው ዮሐንስ ሳህሌን የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርቦለት የሰጠውን ምላሽ ጋዜጣዋ ታቀርብሎታለች፡፡ አሰልጣኝ ዮሐንስ ምን ብሎ ይሆን ሀትሪክን ያንብቧት።
ሀትሪክ ስፖርት በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባዋም ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ፊርማውን ያኖረው ደስታ ደሙ የሚለው አለው። ተከታተሉት፤ ለሌኛው የሸገር ክለብ ኢትዮጵያ ቡናን የተቀላቀለው አለማንተ ካሳ (ማሪዮ) ላይም ሀትሪክ መረጃን ትሰጦታለች፤ ሀትሪክ አታምልጦት፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በባህር ማዶ ዘገባዋም የሚወዱትን ዘገባ አቅርበንሎታል።
የሀትሪክ ስፖርት የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል።
ሀትሪክ ስፖርት በነገው እትሟ የሚወዷት፤ በጉጉት የሚጠብቋት ሳምንታዊዋ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ ማክሰኞም እናንተን በንባብ ልታገኝ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡
Hatricksport team