ከጻውሎስ ጌታቸው(ማንጎ) ጋር የተለያዩት የጣና ሞገዶቹ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት በተጨዋችነት እና በምክትል እሰልጣኝነት በርካታ ዓመታትን ያሳለፈው ፋሲል ተካልኝን በዋና እሰልጣኝነት ለመሾም ተቃርቧል።
በ2010 በጻውሎስ ጌታቸው(ማንጎ) መሪነት ፕሪምየር ሊጉን የተቀላቀሉት የጣና ሞገዶቹ በያዝነው ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴን እሳይተዋል።
በስፔን እና ሃንጋሪን የእግር ኳስ ስልጠናዎችን ተከታትሎ በቅርቡ ወደ እዲስ እበባ የተመለሰው ፋሲል ተካልኝ በቅርብ ቀናት ወደ ባህርዳር በማምራት ለ2012 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዝግጅትና የፊታችን ሐምሌ 26 በሚጀምረው የተጨዋቾች ዝውውር ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።