ተወዳጇ ባለቀለሟ እና ሳምንታዊዋ ጋዜጣዎ ነገ በገበያ ላይ
በሳምንት አንድ ቀን ለንባብ የምትበቃው ተወዳጅ እና ባለቀለሟ የማክሰኞ እትም ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ ማክሰኞም እንደተለመደው ሁሉ ለእናንተ ውድ አንባቢዎቿ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ትቀርባለች፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ነገ ከምታስነብቦት ዘገባ ውስጥ በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ባተረፈላት
THE BIG INTERVIEW አምዷ ወደ ስፔን በመጓዝ የስልጠና ኮርስን ለመውሰድ እየተዘጋጀ የሚገኘውን የቀድሞ የኢትዮጵያ ቡናና የብሄራዊ ቡድናችን ተጨዋች እንደዚሁም ደግሞ የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ የነበረውን እድሉ ደረጄን /በዴክሶ/ ያቀረብንላችሁ ሲሆን እሱም ስለስልጠና ሕይወቱና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ምላሹን ይሰጣል፡፡
ሀትሪክ በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባዋ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የስልጠና ኮርስን ለመውሰድ ወደ ሀንጋሪ ቡዳፔስት ስለማምራቱና ስለሚወስደው ስልጠናም ጥያቄዎች ተነስቶለት እሱም ምላሽን ሰጥቷል፤ ከእዚህ ዘገባ ባሻገር ሀትሪክ ነገ የምታስነብቦት የኢትዮጵያ እና የማሊ ኦሎምፒክ ብሔራዊ ቡድኖች ሐሙስ እለት ስለሚያደርጉት የኦሎምፒክ የማጣሪያ ጨዋታ እና ስለ ኦሎምፒክ ብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅት የቡድኑን ተጨዋች በረከት ደስታን አናግረነው ምላሹን የሰጠበት ይገኛል፡፡
ሀትሪክ ስፖርት በባህር ማዶ ዘገባዋም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግን እና የአውሮፓ የውስጥ ውድድሮችን አስመልክቶ የሚወዱትን ዘገባም ይዛሎት ቀርባለች፤ የነገዋ ሀትሪክ አታምልጦ፡፡
የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የነገ እትም የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል