በካሜሩን አዘጋጅነት ለሚካሄደው የ2020 ቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር ጥቅምት 08/2012ዓ.ም ሩዋንዳ ኪጋሊ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ላለበት የመልስ ጨዋታ ለ24 ተጫዋቾች የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ጥሪ አደረጉ፡፡
የብሔራዊ ቡድኑ አባላትም ማረፊያቸው አዳማ በሚገኘው ኤክሰኪውቲቭ ሆቴል በማድረግ ዝግጅታቸውን ከመስከረም 26/2012ዓ.ም እሰከ ጥቅምት 05/2012ዓ.ም በማድረግ ጥቅምት 6/2012ዓ.ም ወደ ሩዋንዳ በማቅናት ጥቅምተ 8/2012ዓ.ም ከቀኑ 10ሰዓት ሩዋንዳ ኪጋሊ ላይ የመልስ ጨዋታቸውን የሚያከናውኑ ይሆናል፡፡
መስከረም 25/2012ዓ.ም አዳማ ከተማ በሚገኘው ኤኪስኩቲቭ ሆቴል ከቀኑ 8ሰዓት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ዝርዝር የሚከተሉት መሆናቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል፡፡
1 ምንተስኖት አሎ – ግብ ጠባቂ – መከላከያ እግር ኳስ ክለብ
2 ጀማል ጣሰው – ግብ ጠባቂ – ፋሲል ከነማ
3 ለዓለም ብርሃኑ – ግብ ጠባቂ – ቅ/ጊዮርጊስ
4 አስቻለው ታመነ – ተከላካይ – ቅ/ጊዮርጊስ
5 ደስታ ዳሙ – ተከላካይ – ቅ/ጊዮርጊስ
6 ያሬድ ባዬ – ተከላካይ – ፋሲል ከነማ
7 አንተነህ ተስፋዬ – ተከላካይ- መከላከያ እግር ኳስ ክለብ
8 አህመድ ረሺድ – ተከላካይ – ኢትዮጵያ ቡና
9 ጌቱ ኃ/ማሪያም – ተከላካይ – ሰበታ ከተማ
10 መሳይ ጳውሎስ – ተከላካይ – ሐዋሳ ከተማ
11 ረመዳን የሱፍ – ተከላካይ – ስሁል ሽረ
12 አማኑኤል ዮሐንስ – አማካይ – ኢትዮጵያ ቡና
13 ፍጹም አለሙ – አማካይ – ባሕር ዳር ከተማ
14 ሀይደር ሸረፋ – አማካይ – ቅ/ጊዮርጊስ
15 ዮናስ በርታ – አማካይ – አዳማ ከተማ
16 ሱራፌል ዳኛቸው – አማካይ – ፋሲል ከነማ
17 ከነዓን ማርክነህ – አማካይ –
አዳማ ከተማ
18 አስቻለው ግርማ – አጥቂ – ሰበታ ከተማ
19 ፉአድ ፈረጃ – አጥቂ – አዳማ ከተማ
20 መስፍን ታፈሰ – አጥቂ – ሐዋሳ ከተማ
21 አማኑኤል ገ/ሚካኤል – አጥቂ – መቐለ 70 እንድርታ
22 ሙጂብ ቃሲም – አጥቂ – ፋሲል ከነማ
23 ፍቃዱ አለሙ – አጥቂ – መከላከያ
24 አዲስ ግደይ – አጥቂ – ሲዳማ ቡና
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሩዋንዳ አቻው ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ ተደረገ
Hatricksport team