ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ ከ መቐለ ከተማ ጋር የሚያደረገው ተስተካካይ መርሐ ግብር ጨዋታ አዲስአበባ ስታዲየም ላይ እንደማይከናወን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።
ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ ከ መቐለ ከተማ ጋር የሚያደርጉት የተስተካካይ መርሐ ግብር ጨዋታ በአዲስአበባ ስታዲየም የፊታችን አርብ ግንቦት 17 ቀን 2010 እንዲደረግ የኢትዮጵያ እግርኳስ መወሰኑ እሚታወስ ሲሆን ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዮንቨርሲቲ በአንፃሩ ጨዋታው አዲስአበባ ስታዲየም መደረግ ያለበትም በሚል ለፌዴሬሽኑ የቅሬታ ደብዳቤ ማስገባቱ ሲታወቅ ፣ በተጨማሪ
የትግራይ ክልል ኮማንድ ፖስት ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጨዋታውን ለማካሄድ በቂ የፖሊስ ሀይል እንዳለው በላከው ደብዳቤ መግለፁን አስመልክቶ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጨዋታውን በመጪው ግንቦት 17 ቀን 2010 በ9:00 ሰዓት በሸሬ ሜዳ እንዲካሄድ ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል።
![የትግራይ ክልል ኮማንድ ፖስት ለፌዴሬሽኑ የላከው ደብዳቤ](https://i0.wp.com/www.hatricksport.com/wp-content/uploads/2018/05/picsart_05-21-12169362506.jpg?resize=1170%2C1353)
![ወልዋሎ አዲግራት ለፌዴሬሽኑ ያስገባው ደብዳቤ ገፅ-1](https://i0.wp.com/www.hatricksport.com/wp-content/uploads/2018/05/picsart_05-21-121932508588.jpg?resize=1170%2C1776)
![ወልዋሎ አዲግራት ለፌዴሬሽኑ ያስገባው ደብዳቤ ገፅ-2](https://i0.wp.com/www.hatricksport.com/wp-content/uploads/2018/05/picsart_05-21-121464861000.jpg?resize=1170%2C1218)