የጅማ አባ ጅፋር ተጫዋቾች ደሞዛችን አልተከፈለንም በማለት ልምምድ አቁመዋል
ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ በደሞዝ ችግር ምክንያት ልምምድ ማቆማቸው የሚታወስ ሲሆን። በዘንድሮው አመትም ለበርካት ክለቦች ፈተና የሆነው የፋይናንስ ችግር በውድድሩ ጫና እያሳደረባቸው ይገኛል። የዚህ ሰለባ የሆነው ጅማ አባጅፋር ደሞዝ ካልተከፈለን ልምምድ አናደርግም በማለት ተጫዋቾቹ ዋሬ ጥዋት ሊያደርጉ የነበረባቸውን ልምምድ ሳያከናውኑ መቅረታቸውን ነው የሀትሪክ ምንጮች የሚያመላክቱት።