ከወትሮ በተለየ መልኩ በዝዉዉር ገበያዉ ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኙት አዳማ ከተማዎች አሁን ደግሞ የቀድሞ ተጫዋቾቻቸውን አማኑኤል ጎበናን ወደ ስብስባቸዉ መቀላቀል ችለዋል።
የእግርኳስ ሂወቱን በቅዱስ ጊዮርጊስ ወጣት ቡድን የጀመረዉ ተጫዋቹ በአርባምንጭ ከተማ ፤ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ፤ አዳማ ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና መጫወትም ችሏል።
ከቀድሞዉ አሰልጣኙ አሸናፊ በቀለ ጋር በሀድያ ሆሳዕና ቤት መስራት የቻለዉ ተጫዋቹ የዉድድር አመቱን ካሳለፈበት ሀድያ በመልቀቅ የቀድሞ ክለቡን አዳማ ከተማ ሁለት አመት በሚቆይ ዉል ተቀላቅሏል።