አሁን ይፋ በሆነ መረጃ በዋልያዎቹ ምድብ ውስጥ የሚገኙት ኮትዲቯር ወሳኝ ተጫዋች የሆነው ጀርቪንሆ ከ ኒጀር እና ዋልያዎቹ ጨዋታ ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል ።
ጀርቪንሆ ከ ዝሆኖቹ ጋር ያለፉትን ቀናት ልምምድ እየሰራ ቢቆይም በዛሬው ዕለት የጭን ጉዳት ማስተናገዱን ተከትሎ ጨዋታዎቹ እንደሚያመልጡት ይፋ ተደርጓል ።
የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ጀርቪንሆን ጨምሮ ሴባስቲያን ሀለር እንዲሁም ሰርጂ ኦሪየር በአጠራጣሪ ሁኔታ ላይ ቢሆን ጨዋታው እንደሚያመልጣቸው ታውቋል ።