በኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ በከፍተኛ ጎል አግቢዋች ደረጃ ለ16 አመታት ሪከርዱን ማስደፈር ያልተቻለው የድሬዳዋው ልጅ ዮርዳኖስ አባይ ሲሆን በ1993 በኢትዮ-ኤሌትሪክ እግር ኳስ ክለብ 24 ጎሎችን በማስቆጠር ለ16አመት ሪከርዱ ሳይነካበተ ቆይቶል፡፡በአሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሊግ ላይ በመወዳደር እሚገኘው የናሽናል ሲሜንት እግር ኳስ ክለብ የቡድን መሪ በመሆን እየሰራ ይገኛል፡፡ ከሀትሪክ ስፖርት ድህረ -ገፅ ጋር የከፍተኛ ጎል አግቢ ደረጃውን እየመራ ሪከርዱን ለመጋራት ወይም ለመስበር እየገሰገስ ስለ ሚገኘው ጌታነህ ከበደ አስተያየቱን ሰጧል፡፡
በ1993 በ 24 ጎል የያዝከው፡ሪከርድ ቢሰበር ምን ይሰማሀል?
ዮርዳኖስ፡-ሁልግዜ ንግስና የለም ሪከርዱ ተሰብሮ ባይ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
- ማሰታውቂያ -
የደደቢት እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ጌታነህ ከበደን እንዴት ትገልፀዋለህ?
ዮርዳኖስ:- ጌታነህ ከበደ በቅርብ አመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ከታዪ ምርጥ አጥቂዎች ውስጥ ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ ጎል ላይ ሲደርስ ያለው የውሳኔ ፍጥነት ያስገርመኛል፡፡ ከዚህም በተሻለ የመጫወት ብቃት አለው፡፡ ሲል ለሀትሪክ ስፖርት ድህረገጽ አስተያየቱን ሰጧል፡፡