ኢትዮጵያ በቀጣዩ የፈረንጆቹ ዓመት የሚካሄደውን የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር /ፊፋ. ጠቅላላ ጉባኤን እንድታስተናግድ ተመረጠች።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው አገሪቱ ጉባኤን እንድታስተናግድ የተመረጠችው ባለፈው ሳምንት ሜክሲኮ ላይ በተካሄደው የማህበሩ 66ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ነው።
በዚህ ጉባኤ ላይ በተጨማሪም በአዲስ አበባ ለሚከፈተው እና በጅምር ላይ ላለው የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል የሚሆን የ4 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀትን ፊፋ አፅድቋል።
ኢትዮጵያ በምታስተናግደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከ209 አገራት የተውጣጡ የፊፋ አባል ብሄራዊ የእግር ኳስ ማህብራት ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ በቀጣዩ የፈረንጆቹ ዓመት የሚካሄደውን የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር /ፊፋ. ጠቅላላ ጉባኤን እንድታስተናግድ ተመረጠች
![](https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2016/08/5432345676543456768743.jpg?resize=480%2C326&ssl=1)
Hatricksport team