ከትውልደ ኢትዮጵያወያኑ እናት እና አባት የተወለደው የ 20 ዓመት ወጣቱ የመስመር ተጫዋች ዮናስ ከእስራኤሉ ክለብ ማካቢ ኔታንያ ወደ ቤልጅዬሙ ጌንት ክለብ ለአራት ዓመታት ለመጫወት መስማማቱ ይፋ ሆኗል ።
• ዮናስ ማለደ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ከቀኝ መስመር እየተነሳ በአስራ አምስት ጨዋታዎች ሰባት ጎሎችን አስቆጥሮ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል ።
• ዮናስ ከቀናት በፊት በይፋ ፊርማውን ሲያኖር የክለቡ ስፖርት ሀላፊ ከፊርማው ስነ-ስርዓት በኋላ ዪናስ ፈጣን እና ከመስመር እየተነሱ ከመጫወት አልፎ በሀሰተኛ ዘጠኝ ቁጥር ጥሩ የመጫወት አቅም እንዳለው ገልፀዋል ።