ሀትሪክ በነገው እትሟ
ባለቀለሟ እና ተወዳጅ የሆነችው ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣችን ነገ ማክሰኞም ከእጅዎ ልትገባ መሰናዶዋን አጠናቅቃለች፡፡
ሀትሪክ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ወጥታ ይሆን?
-ከሀገር ውስጥ፡- በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የእዚህ ሳምንት ጨዋታ ፋሲል ከነማ ጅማ አባጅፋርን በሰፊ ግብ አሸንፎ የሊጉን መሪነት ከመቀለ 70 እንደርታ በመርከቡ ዙሪያ ለቡድኑ እስካሁን አስራሁለት ጎል ያስቆጠረው ሙጂብ ቃሲም አናግረነው ምላሹን ሰጥቷል ፡፡
በካናዳ ኦታዋ ማራቶን ኢትዮጵያን አትሌቶች ስለሚሳተፉበት ውድድር ጥልቅ ዘገባ አላት።
ሀትሪክ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈችበት THE BIG INTERVIEW አምድ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ማህበር ፕረዚዳንት መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ ጋር ቆይታ አድርጋለች። መቶ አለቃ ምን ብለው ይሆን? የነገዋን ሀትሪክ ያንብቧት።
ከባህር ማዶ፡- የእንግሊዝ ኘሪሜየር ሊግ መጠናቀቁን ተከትሎ ዘንድሮ ምርጥ ብቃቱን ስላሳየው የማንቸስተር ሲቲው ራሂም ስተርሊንግ ሰፋ ያለ ዘገባ ያቀረብንላቸው ሲሆን ከዛ ውጪ አነጋጋሪ አስተያየቶችን በመስጠት እሚታወቁት ጆሴ ሞሪንሆ ወቅታዊው ስለሆነው የማንቸስተር ዮናይትድ ችግሮች ይናገራሉ።
- ማሰታውቂያ -
እናም ሌሎች ያልተሰሙ አዳዲስና ትኩስ ዘገባዎችን ነገ ማለዳ ይዛ እጅዎ ትገባለች፡፡
በርካታ አንባቢዎቻችን ባቀረባችሁልን ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት ሀትሪክን በሳምንት ሁለት ቀን በቅርቡ ይዘን እንቀርባለንና ጠብቁን፡፡ ተጨማሪና ትኩስ መረጃዎችን በርካታ ተከታታዮች ባሉት hatricksport.com ድረ-ገፃችን ይጎብኙን፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፡፡
መልካም ንባብ