የሄንግሎ የዕለቱ መርሐ ግብር የመጨረሻ ውድድር በነበረው የ ሴቶች 10,000 ሜትር ውድድር ኢትዮጵያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ የሚሳተፉ አትሌቶቿን ለይታለች ።
በሴቶች 10,000 ሜትር በተካሄደ ውድድር የተሳካ ጊዜን እያሳለፈች የምትገኘው ለተሰንበት ግደይ ድንቅ ብቃቷን በማሳየት ውድድሯን 29:01.03 በሆነ ደቂቃ በመግባት በበላይነት በማጠናቀቅ ኢትዮጵያን በ ኦሎምፒክ እንደምትወክል ከማረጋገጥ ባለፈ ሪከርዱን የግሏ ማድረግ ችላለች ።
በውድድሩ ከቀናት በፊት በ ሲፋን ሀሰን የተሰበረውን የ 10,000 ሜትር ሪከርድ ቀናቶች ሳይቆጠሩ ሪከርዱ በኢትዮጵያ ስር እንዲሆን አድርጋለች ።