ሳምንታዊ ባለቀለም የስፖርት ጋዜጣ የሆነችው ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ እንደተለመደው ሁሉ ነገም ማክሰኞ ታህሳስ 10/2010 ዓ.ም በማለዳው በእጅዎ ልትገባ መሰናዶዋን አጠናቅቃለች፡፡
ለመሆኑ ምን ምን ጉዳዮችን ይዛ ይሆን?
-ከሀገር ውስጥ፡- በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 7ኛ ሳምንት ሀትሪክ መስራት የቻለው የደደቢቱ ወጣት አጥቂ አቤል ያለው ማስመዝገብ ስለሚፈልጋቸው የግል ስኬቶች ከክለቡ ጋር ዋንጫ ስለማንሳት እና ሌሎች ብዙ ሀሳቦችን በማንሳት ከሀትሪክ ስፖርት ጋር ጣፋጭ ቆይታ አድርጓል።
ወጣቱ እና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ለክለቡም ሆነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ድንቅ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘው የቅ/ጊዮርጊሱ አቡበከር ሳኒ ሌላው ታፋጭ እና አጓጊ ቆይታን ያደረገ ተጨዋች ነው።
ከባህር ማዶ፡- የማንችስተር ሲቲ የማይገታ የሚመስለው ጉዞና የኬቨን ደብሮይነ ድንቅ ብቃት የታየበት ጨዋታ፣ ጎል ካስቆጠረ በኋላ መደሰት ስላቆመው የማንቸስተር ዩናይትዱ አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ እንዲሁም አርሰን ቬንገር በኦዚል ጎል ማግባት መደሰታቸውን እና በአርሰናል እንደሚቆይ ተስፋ ማድረጋቸውን በስፋት ዳሰነዋል።
በኦልዲስ በት ጉዲስ አምዳችን ደግሞ ለሁለቱም ታላላቅ ቡድኖች ኢት. ቡና እና ቅ/ጊዮርጊስ የተጫወተው እና የቅጣት ምቱ ንጉስ በመባል ከሚታወቀው ሰለሞን ግርማ(ልምጭ) ጋር ሰፋ ያለ ቆይታ አድርገናል።
እናም ሌሎች ያልተሰሙ አዳዲስና ትኩስ ዘገባዎችን ነገ ማለዳ ይዛ እጅዎ ትገባለች፡፡
በርካታ አንባቢዎቻችን ባቀረባችሁልን ተደጋጋሚ ጥያቄ መሰረት ሀትሪክን በሳምንት ሁለት ቀን በቅርቡ ይዘን እንቀርባለንና ጠብቁን፡፡ ተጨማሪና ትኩስ መረጃዎችን በርካታ ተከታታዮች ባሉት hatricksport.com ድረ-ገፃችን ይጎብኙን፡፡
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል፡፡
መልካም ንባብ