በ2011 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከወራጅነት ለጥቂት የተረፈው ስሑል ሽረ የቀጣይ ውድድር ዓመት ዝግጅቱን ሥስት ተጨዋቾችን በማስፈረም ጀምሯል።
ባለፈው የውድድር ዓመት የግብ ጠባቂ ችግር የተስተዋለበት ስሑል ሽረ ወንድወሰን እሸናፊን ከኢትዮጵያ ቡና እስፈርሟል።የቀድሞው የወላይታ ድቻ እና ኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ ወንድወሰን እሸናፊ ባሳለፍነው ዓመት ከኢትዮጵያ ቡና ተቀያሪ ወንበር እየተነሳ እንዳንድ ጨዋታዎችን እካሂዷል።
በተመሳሳይ የተከላካይ መስመራቸውን ለማጠናከር በረከት ተሰማን ከወልዋሎ እብዲ ማሳላቺን ከጋና እስፈርሟል።የወልዋሎ ተከላካይ ክፍልን ከቢንያም ስራጅ ጋር በመፈራረቅ የመራው በርከት በቀጣይ ዓመት በስሑላውያን ማልያ ምንመለከተው ይሆናል።
- ማሰታውቂያ -
በ2010 ለመቐለ 70 እንደርታ ፈርሞ ምንም ጨዋታ ሳያደርግ ወደ ሃገሩ የተመለሰውን የተከላካይ መስመር ተሰላፊው እዳሙ ማሳላቺን እስፈርሟል።