አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ የኢትዮጵያ ሴቶች የኦሎምፒክ እግር ኳስ ቡድን ከካሜሩን ጋር ላለበት ጨዋታ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አድርጋለች፡፡
የኢትዮጵያ ሴት ኦሎምፒክ እግር ኳስ ቡድን ከካሜሩን አቻው ጋር የኦሎምፒክ ማጣሪያ ጨዋታውን ነሃሴ 20/2011ዓ.ም በባህር ዳር ኢንተርናሽናል ስታዲየም ያካሂዳል፡፡ ለዚህም እንዲረዳት አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አድጋለች፡፡
ጥሪ የተደረገላው ተጫዋቾች በነገው ዕለት ነሃሴ 1/2011ዓ.ም አዲስ አበባ ስታዲየም ቴክኒክ እና ልማት ዳይሬክቶሬት ከጠዋቱ 4 ሰዓት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፎላቸዋል፡፡
ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች
- ማሰታውቂያ -
ግብ ጠባቂዎች
ታሪኳ በርገና (ጥረት ኮርፖሬት)
አባይነሽ ኤርቄሎ (ሀዋሳ ከተማ)
ማርታ በቀለ (መከላከያ)
ተከላካዮች
መስከረም ኮንካ ( አዳማ ከተማ)
ገነሜ ወርቁ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
መሰሉ አበራ (መከላከያ)
ቅድስት ዘለቀ (ሐዋሳ ከተማ)
ብዙዓየሁ ታደሰ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
ናርዶስ ጌትነት (አዳማ ከተማ)
አለምነሽ ገረመው (ኢትዮ ኤሌክተሪክ)
ነጻነት ጸጋዬ (አዳማ ከነማ)
አማካኞች
እጸገነት ብዙነህ (አዳማ ከነማ)
ሕይወት ደንጌሶ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
እመቤት አዲሱ(መከላከያ)
ብርቱካን ገ/ክርስቶስ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
ሰናይት ቦጋለ (አዳማ ከተማ)
አረጋሽ ካልሳ (መከላከያ)
አጥቂዎች
ምርቃት ፈለቀ(ሐዋሳ ከተማ)
ሎዛ አበራ(አዳማ ከተማ)
መዲና ጀማል( ሀዋሳ ከተማ)
ሴናፍ ዋቁማ (አዳማ ከተማ)
ሰርካዲስ ጉታ (አዳማ ከነማ)
ሔለን እሸቱ
ምንጭ – የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን