-የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ስርቪስ መኪና የመገልበጥ አደጋ ደረሰበት! ከአዲስ አበባ ወደ ሐዋሳ ሲጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ
መኪና ዝዋይ ላይ ሲደርስ አደጋ አጋጥሞታል። የስፖርት ክለቡ በፌስ ቡክ ገፁ አደጋውን አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል፡፡
” መኪናዋን ሲያሽከረክር የነበረው ሾፌር መጠነኛ ጉዳትና የንብረት ጉዳት ሲደርስ – የቡድናችን ዋና አሠልጣኝ ነቦይሻ ቪችቼቪች(ኦሽኬ) እንዲሁም ቴክኒካል ዳይሬክተሩ አቶ ደምሰው ፍቃዱ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው ሐዋሳ ከሚገኘው ቡድን ጋር ተቀላቅለዋል “