ባለፈው ዓመት መቐለ 70 እንደርታን በመልቀቅ የግብፁ አዲስ ያደገውን ኤልጉናን የተቀላቀለው ጋቶች ፓኖም ከአንድ ዓመት ቆይታ በኃላ ከክለቡ ጋር ተለያይቷል።
ኤልጉና ላለመውረድ ባደረገው ከፍተኛ ተጋድሎ የራሱን ድርሻ የተጫወተው ግዙፋ አማካይ ጋቶች ከክለቡ ጋር ቀሪ የሁለት ዓመት ኮንትራት እያለለው ክለቡን በስምምነት ሊለቅ ችሏል።
የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና፣መቐለ 70 እንደርታ፣አንዚ ማካቻካላ እና ኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እማካይ ጋቶች ፓኖም በተጠናቀቀው የግብፅ ሊግ እንድ ግብ ማስቆጠር ችሏል።የጋቶች ቀጣይ ማረፍያ ክለብ ከኢትዮጵያ ውጪ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።