ለካሳዬ አራጌ የጨዋታ ስልት ይሆናሉ የተባሉ ተጨዋቾቹን በማስፈረም ላይ ሚገኙት ቡናዎች ፈቱዲን ጀማልን ከሲዳማ ቡና አስፈርመዋል።
ሲዳማ ቡና በዘርአይ ሙሉ እየተመራ ለዋንጫ በተፎካከረበት የ2011 ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የቡድኑን ተከላካይ ክፍል በሚገባ በመምራት ብቃቱን ያሳየው ፈቱዲን ጀማል ለኢትዮጵያ ቡና ፌራማውን አኑሯል።
የቀድሞው የሃላባ ከተማና ወላይታ ድቻ ተጨዋች ፈቱዲን ጀማል በአብርሃም መብራህቱ ጥሪ ተደርጎለት ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ኦሎምፒክ ቡድን መጫወት ችሏል።