የአዲስአበባ ከተማ ዋንጫ የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስረዓት በኢትዮጵያ ሆቴል በዛሬው እለት ተካሂዷል፡፡
በስነስርዓቱ ላይ የተለያዩ ሀሳቦች ከክለብ ተወካዮች የቀረበ ሲሆን ስምንት ክለቦችን በሚያሳተፍ ውድድር ምድቡ በሁለት ተከፍሎ በምድብ አባቶች ስር እንዲካሄድ ሀሳብ ቀርቦ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሌሎች ክለቦች እጣ በወጣላቸው የምድብ አባት ስር ተደልድለዋል፡፡
የምድብ አባቶች ሆነው የተመረጡት በምድብ-ሀ ኢትዮጵያ ቡና ሲሆን በምድብ-ለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆነው በሁለት ምድብ ተከፍለዋል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች እንዴት ተመረጡ ለሚለው ጥያቄ ባላቸው የደጋፊ ብዛት እንደ ተመረጡ አዘጋጆች ገልፀዋል፡፡
በዚሁ መሠረት
በምድብ- ሀ
- ማሰታውቂያ -
ኢትዮጵያ ቡና
ደደቢት
አዲስአበባ ከተማ
ጅማ አባጅፋር
በምድብ-ለ
ቅዱስ ጊዮርጊስ
አዳማ ከተማ
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ
መከላከያ
የአዲስ አበባ ሲቲ ካኘ መስከረም 28 ሰኞ እለት ሲጀምር:- በ8ሰዓት
ደደቢት ከ አዲስአበባ ከተማ
በ10ሰዓት
ኢትዮጵያ ቡና ከ ጅማ አባጅፋር
ይጫወታሉ፡፡ በቀጣዩ ቀን ጨዋታው ሲቀጥል
በ9ሰዓት
አዳማ ከተማ ከ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ
በ11 ሰዓት
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መከላከያ
እሚጫወቱ ይሆናል፡፡